العاديات

تفسير سورة العاديات

الترجمة الأمهرية

አማርኛ

الترجمة الأمهرية

ترجمة معاني القرآن الكريم للغة الامهرية ترجمها الشيخ محمد صادق ومحمد الثاني حبيب . الطبعة 2011م. ملاحظة: ترجمات بعض الآيات (مشار إليها) تم تصويبها بمعرفة مركز رواد الترجمة، مع إتاحة الاطلاع على الترجمة الأصلية لغرض إبداء الرأي والتقييم والتطوير المستمر.

﴿بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَٰنِ الرَّحِيمِ وَالْعَادِيَاتِ ضَبْحًا﴾

እያለከለኩ ሩዋጮች በኾኑት (ፈረሶች) እምላለሁ፡፡

﴿فَالْمُورِيَاتِ قَدْحًا﴾

(በሰኮናቸው) እያጋጩ እሳትን አውጪዎች በኾኑትም፤

﴿فَالْمُغِيرَاتِ صُبْحًا﴾

በማለዳ ወራሪዎች በኾኑትም፤

﴿فَأَثَرْنَ بِهِ نَقْعًا﴾

በእርሱ አቧራን በቀሰቀሱትም፤

﴿فَوَسَطْنَ بِهِ جَمْعًا﴾

በ(ጠላት) ክቢ መካከል በእርሱ (በጧት) በተጋፈጡትም እምላለሁ፡፡

﴿إِنَّ الْإِنْسَانَ لِرَبِّهِ لَكَنُودٌ﴾

ሰው ለጌታው ብርቱ ከሓዲ ነው፡፡

﴿وَإِنَّهُ عَلَىٰ ذَٰلِكَ لَشَهِيدٌ﴾

እርሱም በዚህ ላይ መስካሪ ነው፡፡

﴿وَإِنَّهُ لِحُبِّ الْخَيْرِ لَشَدِيدٌ﴾

እርሱም ገንዘብን ለመውደድ በጣም ብርቱ ነው፡፡

﴿۞ أَفَلَا يَعْلَمُ إِذَا بُعْثِرَ مَا فِي الْقُبُورِ﴾

(ሰው) አያውቅምን? በመቃብሮች ያሉት (ሙታን) በተቀሰቀሱ ጊዜ፤

﴿وَحُصِّلَ مَا فِي الصُّدُورِ﴾

በልቦች ውስጥ ያለውም ሁሉ በተገለጸ ጊዜ (እንዴት እንደሚኾን)፡፡

﴿إِنَّ رَبَّهُمْ بِهِمْ يَوْمَئِذٍ لَخَبِيرٌ﴾

ጌታቸው በዚያ ቀን በእነርሱ (ነገር) በእርግጥ ውስጠ አዋቂ ነው፡፡

الترجمات والتفاسير لهذه السورة: