النازعات

تفسير سورة النازعات

الترجمة الأمهرية

አማርኛ

الترجمة الأمهرية

ترجمة معاني القرآن الكريم للغة الامهرية ترجمها الشيخ محمد صادق ومحمد الثاني حبيب . الطبعة 2011م. ملاحظة: ترجمات بعض الآيات (مشار إليها) تم تصويبها بمعرفة مركز رواد الترجمة، مع إتاحة الاطلاع على الترجمة الأصلية لغرض إبداء الرأي والتقييم والتطوير المستمر.

﴿بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَٰنِ الرَّحِيمِ وَالنَّازِعَاتِ غَرْقًا﴾

በኃይል አውጪዎች በኾኑት፤

﴿وَالنَّاشِطَاتِ نَشْطًا﴾

በቀስታ መምዘዝንም መዘዦች በኾኑት፤

﴿وَالسَّابِحَاتِ سَبْحًا﴾

መዋኘትም ዋኚዎች በኾኑት፤

﴿فَالسَّابِقَاتِ سَبْقًا﴾

መቅደምንም ቀዳሚዎች በኾኑት፤

﴿فَالْمُدَبِّرَاتِ أَمْرًا﴾

ነገርንም አስተናባሪዎች በኾኑት (መላእክት) እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡

﴿يَوْمَ تَرْجُفُ الرَّاجِفَةُ﴾

ተርገፍጋፊይቱ (ምድር) በምትርገፈገፍበት ቀን፤

﴿تَتْبَعُهَا الرَّادِفَةُ﴾

ለጣቂይቱ የምትከተላት ስትኾን (ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡

﴿قُلُوبٌ يَوْمَئِذٍ وَاجِفَةٌ﴾

በዚያ ቀን ልቦች ተሸባሪዎች ናቸው፡፡

﴿أَبْصَارُهَا خَاشِعَةٌ﴾

ዓይኖቻቸው ተዋራጆች (አቀርቃሪዎች) ናቸው፡፡

﴿يَقُولُونَ أَإِنَّا لَمَرْدُودُونَ فِي الْحَافِرَةِ﴾

«እኛ ወደ መጀመሪያይቱ ኹነታ ተመላሾች ነን?» ይላሉ፡፡

﴿أَإِذَا كُنَّا عِظَامًا نَخِرَةً﴾

«የበሰበሱ አጥንቶች በኾን ጊዜ (እንቀሰቀሳለን?)»

﴿قَالُوا تِلْكَ إِذًا كَرَّةٌ خَاسِرَةٌ﴾

«ይህቺ ያን ጊዜ ባለ ከሳራ መመለስ ናት» ይላሉ፡፡

﴿فَإِنَّمَا هِيَ زَجْرَةٌ وَاحِدَةٌ﴾

እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡

﴿فَإِذَا هُمْ بِالسَّاهِرَةِ﴾

ወዲያውኑም እነርሱ እንቅልፍ በሌለባት (ምድር) ላይ ይኾናሉ፡፡

﴿هَلْ أَتَاكَ حَدِيثُ مُوسَىٰ﴾

የሙሳ ወሬ መጣልህን?

﴿إِذْ نَادَاهُ رَبُّهُ بِالْوَادِ الْمُقَدَّسِ طُوًى﴾

ጌታው በተቀደሰው ሸለቆ በጡዋ በጠራው ጊዜ፤

﴿اذْهَبْ إِلَىٰ فِرْعَوْنَ إِنَّهُ طَغَىٰ﴾

ወደ ፈርዖን ኺድ፡፡ እርሱ ወሰን አልፏልና፡፡

﴿فَقُلْ هَلْ لَكَ إِلَىٰ أَنْ تَزَكَّىٰ﴾

በለውም፡- «ወደ መጥራራትህ ላንተ (መንገድ) አለህን?»

﴿وَأَهْدِيَكَ إِلَىٰ رَبِّكَ فَتَخْشَىٰ﴾

«ወደ ጌታህም ልመራህ ትፈራውም ዘንድ፤ (መንገድ አለህን?)» አለው፡፡

﴿فَأَرَاهُ الْآيَةَ الْكُبْرَىٰ﴾

ታላቂቱንም ተዓምር አሳየው፡፡

﴿فَكَذَّبَ وَعَصَىٰ﴾

አስተባበለም፤ አመጸም፡፡

﴿ثُمَّ أَدْبَرَ يَسْعَىٰ﴾

ከዚያም (ለማጥፋት) የሚተጋ ኾኖ ዞረ፡፡

﴿فَحَشَرَ فَنَادَىٰ﴾

(ሰራዊቶቹን) ሰበሰበም፤ ተጣራም፡፡

﴿فَقَالَ أَنَا رَبُّكُمُ الْأَعْلَىٰ﴾

አለም፡- «እኔ ታላቁ ጌታችሁ ነኝ፡፡»

﴿فَأَخَذَهُ اللَّهُ نَكَالَ الْآخِرَةِ وَالْأُولَىٰ﴾

አላህም በኋለኛይቱና በፊተኛይቱ (ቃል) ቅጣት ያዘው፡፡

﴿إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَعِبْرَةً لِمَنْ يَخْشَىٰ﴾

በዚህ ውስጥ ለሚፈራ ሰው በእርግጥ መገምገሚያ አለበት፡፡

﴿أَأَنْتُمْ أَشَدُّ خَلْقًا أَمِ السَّمَاءُ ۚ بَنَاهَا﴾

ባፈጣጠር እናንተ ይበልጥ የበረታችሁ ናችሁን? ወይንስ ሰማይ? (አላህ) ገነባት፡፡

﴿رَفَعَ سَمْكَهَا فَسَوَّاهَا﴾

ከፍታዋን አጓነ፤ አስተካከላትም፡፡

﴿وَأَغْطَشَ لَيْلَهَا وَأَخْرَجَ ضُحَاهَا﴾

ሌሊቷንም አጨለመ፡፡ ቀንዋንም ገለጸ፡፡

﴿وَالْأَرْضَ بَعْدَ ذَٰلِكَ دَحَاهَا﴾

ምድርንም ከዚህ በኋላ ዘረጋት፡፡

﴿أَخْرَجَ مِنْهَا مَاءَهَا وَمَرْعَاهَا﴾

ውሃዋንና ግጦሿን ከእርሷ አወጣ፡፡

﴿وَالْجِبَالَ أَرْسَاهَا﴾

ጋራዎችንም አደላደላቸው፡፡

﴿مَتَاعًا لَكُمْ وَلِأَنْعَامِكُمْ﴾

ለእናንተና ለእንስሶቻችሁ መጣቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን አደረገ)፡፡

﴿فَإِذَا جَاءَتِ الطَّامَّةُ الْكُبْرَىٰ﴾

ታላቂቱም መዐት በመጣች ጊዜ፣

﴿يَوْمَ يَتَذَكَّرُ الْإِنْسَانُ مَا سَعَىٰ﴾

ሰው ሁሉ የሠራውን በሚያስታውስበት ቀን፣

﴿وَبُرِّزَتِ الْجَحِيمُ لِمَنْ يَرَىٰ﴾

ገሀነምም ለሚያይ ሰው በተገለጠች ጊዜ፣

﴿فَأَمَّا مَنْ طَغَىٰ﴾

የካደ ሰውማ፣

﴿وَآثَرَ الْحَيَاةَ الدُّنْيَا﴾

ቅርቢቱንም ሕይወት የመረጠ፣

﴿فَإِنَّ الْجَحِيمَ هِيَ الْمَأْوَىٰ﴾

ገሀነም እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡

﴿وَأَمَّا مَنْ خَافَ مَقَامَ رَبِّهِ وَنَهَى النَّفْسَ عَنِ الْهَوَىٰ﴾

በጌታው ፊት መቆምን የፈራ ሰውማ ነፍሱንም ከዝንባሌዋ የከለከለ

﴿فَإِنَّ الْجَنَّةَ هِيَ الْمَأْوَىٰ﴾

ገነት እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡

﴿يَسْأَلُونَكَ عَنِ السَّاعَةِ أَيَّانَ مُرْسَاهَا﴾

«ከሰዓቲቱ መቼ ነው መኾኛዋ?» ሲሉ ይጠይቁሃል፡፡

﴿فِيمَ أَنْتَ مِنْ ذِكْرَاهَا﴾

አንተ እርሷን ከማስታወስ በምን ውስጥ ነህ?

﴿إِلَىٰ رَبِّكَ مُنْتَهَاهَا﴾

(የዕውቀት) መጨረሻዋ ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡

﴿إِنَّمَا أَنْتَ مُنْذِرُ مَنْ يَخْشَاهَا﴾

አንተ የሚፈራትን ሰው አስፈራሪ ብቻ ነህ፡፡

﴿كَأَنَّهُمْ يَوْمَ يَرَوْنَهَا لَمْ يَلْبَثُوا إِلَّا عَشِيَّةً أَوْ ضُحَاهَا﴾

እነርሱ በሚያዩዋት ቀን ያንዲት ቀን ምሽትን ወይም ረፏዷን እንጅ ያልቆዩ ይመስላሉ፡፡

الترجمات والتفاسير لهذه السورة: