المطفّفين

تفسير سورة المطفّفين

الترجمة الأمهرية

አማርኛ

الترجمة الأمهرية

ترجمة معاني القرآن الكريم للغة الامهرية ترجمها الشيخ محمد صادق ومحمد الثاني حبيب . الطبعة 2011م. ملاحظة: ترجمات بعض الآيات (مشار إليها) تم تصويبها بمعرفة مركز رواد الترجمة، مع إتاحة الاطلاع على الترجمة الأصلية لغرض إبداء الرأي والتقييم والتطوير المستمر.

﴿بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَٰنِ الرَّحِيمِ وَيْلٌ لِلْمُطَفِّفِينَ﴾

ለሰላቢዎች ወዮላቸው፡፡

﴿الَّذِينَ إِذَا اكْتَالُوا عَلَى النَّاسِ يَسْتَوْفُونَ﴾

ለእነዚያ ከሰዎች ባስሰፈሩ ጊዜ የሚያስሞሉ፡፡

﴿وَإِذَا كَالُوهُمْ أَوْ وَزَنُوهُمْ يُخْسِرُونَ﴾

ለእነርሱም (ለሰዎቹ) በሰፈሩ ወይም በመዘኑላቸው ጊዜ የሚያጎድሉ (ለኾኑት)፡፡

﴿أَلَا يَظُنُّ أُولَٰئِكَ أَنَّهُمْ مَبْعُوثُونَ﴾

እነዚያ እነርሱ ተቀስቃሾች መኾናቸውን አያውቁምን?

﴿لِيَوْمٍ عَظِيمٍ﴾

በታላቁ ቀን፡፡

﴿يَوْمَ يَقُومُ النَّاسُ لِرَبِّ الْعَالَمِينَ﴾

ሰዎች ሁሉ ለዓለማት ጌታ (ፍርድ)፤ በሚቆሙበት ቀን (ተቀስቃሾች መኾናቸውን)፡፡

﴿كَلَّا إِنَّ كِتَابَ الْفُجَّارِ لَفِي سِجِّينٍ﴾

በእውነት የከሓዲዎቹ (የሰላቢዎቹ) መጽሐፍ በእርግጥ በሲጂን ውስጥ ነው፡፡

﴿وَمَا أَدْرَاكَ مَا سِجِّينٌ﴾

ሲጂንም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?

﴿كِتَابٌ مَرْقُومٌ﴾

የታተመ መጽሐፍ ነው፡፡

﴿وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِلْمُكَذِّبِينَ﴾

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

﴿الَّذِينَ يُكَذِّبُونَ بِيَوْمِ الدِّينِ﴾

ለእነዚያ በፍርዱ ቀን ለሚያስተባብሉት፡፡

﴿وَمَا يُكَذِّبُ بِهِ إِلَّا كُلُّ مُعْتَدٍ أَثِيمٍ﴾

በእርሱም ወሰን አላፊ ኀጢአተኛ ሁሉ እንጅ ሌላ አያስተባብልም፡፡

﴿إِذَا تُتْلَىٰ عَلَيْهِ آيَاتُنَا قَالَ أَسَاطِيرُ الْأَوَّلِينَ﴾

አንቀጾቻችን በእርሱ ላይ በተነበቡ ጊዜ «የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች ናቸው» ይላል፡፡

﴿كَلَّا ۖ بَلْ ۜ رَانَ عَلَىٰ قُلُوبِهِمْ مَا كَانُوا يَكْسِبُونَ﴾

ይከልከል፤ ይልቁንም በልቦቻቸው ላይ ይሠሩት የነበሩት (ኀጢአት) ደገደገባቸው፡፡

﴿كَلَّا إِنَّهُمْ عَنْ رَبِّهِمْ يَوْمَئِذٍ لَمَحْجُوبُونَ﴾

ይከልከሉ፤ እነርሱ በዚያ ቀን ከጌታቸው (ማየት) ተጋራጆች ናቸው፡፡

﴿ثُمَّ إِنَّهُمْ لَصَالُو الْجَحِيمِ﴾

ከዚያም እነርሱ በእርግጥ ገሀነምን ገቢዎች ናቸው፡፡

﴿ثُمَّ يُقَالُ هَٰذَا الَّذِي كُنْتُمْ بِهِ تُكَذِّبُونَ﴾

ከዚያም «ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉበት የነበራችሁት ነው» ይባላሉ፡፡

﴿كَلَّا إِنَّ كِتَابَ الْأَبْرَارِ لَفِي عِلِّيِّينَ﴾

በእውነቱ የእውነተኞቹ ምእምናን መጽሐፍ በዒሊዮን ውስጥ ነው፡፡

﴿وَمَا أَدْرَاكَ مَا عِلِّيُّونَ﴾

ዒሊዮንም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?

﴿كِتَابٌ مَرْقُومٌ﴾

የታተመ መጽሐፍ ነው፡፡

﴿يَشْهَدُهُ الْمُقَرَّبُونَ﴾

ባለሟልዎቹ ይጣዱታል፡፡

﴿إِنَّ الْأَبْرَارَ لَفِي نَعِيمٍ﴾

እውነተኞቹ ምእምናን በእርግጥ በድሎት (ገነት) ውስጥ ናቸው፡፡

﴿عَلَى الْأَرَائِكِ يَنْظُرُونَ﴾

በባለ አጎበር አልጋዎች ላይ ኾነው ይመለከታሉ፡፡

﴿تَعْرِفُ فِي وُجُوهِهِمْ نَضْرَةَ النَّعِيمِ﴾

በፊቶቻቸው ላይ የድሎትን ውበት ታውቃለህ፡፡

﴿يُسْقَوْنَ مِنْ رَحِيقٍ مَخْتُومٍ﴾

ተጣርቶ ከታተመ ጠጅ ይጠጣሉ፡፡

﴿خِتَامُهُ مِسْكٌ ۚ وَفِي ذَٰلِكَ فَلْيَتَنَافَسِ الْمُتَنَافِسُونَ﴾

ማተሚያው ምስክ ከኾነ፤ በዚህም ተሽቀዳዳሚዎች ይሽቀዳደሙ፡፡

﴿وَمِزَاجُهُ مِنْ تَسْنِيمٍ﴾

መበረዣውም ከተስኒም ነው፡፡

﴿عَيْنًا يَشْرَبُ بِهَا الْمُقَرَّبُونَ﴾

ባለሟሎቹ ከእርሷ የሚጠጡላት ምንጭ ናት፡፡

﴿إِنَّ الَّذِينَ أَجْرَمُوا كَانُوا مِنَ الَّذِينَ آمَنُوا يَضْحَكُونَ﴾

እነዚያ ያምመጹት በእነዚያ ባመኑት በእርግጥ ይስቁ ነበሩ፡፡

﴿وَإِذَا مَرُّوا بِهِمْ يَتَغَامَزُونَ﴾

በእነርሱም ላይ ባለፉ ጊዜ ይጠቃቀሱ ነበር፡፡

﴿وَإِذَا انْقَلَبُوا إِلَىٰ أَهْلِهِمُ انْقَلَبُوا فَكِهِينَ﴾

ወደ ቤተሰቦቻቸውም በተመለሱ ጊዜ (በመሳለቃቸው) ተደሳቾች ኾነው ይመለሱ ነበር፡፡

﴿وَإِذَا رَأَوْهُمْ قَالُوا إِنَّ هَٰؤُلَاءِ لَضَالُّونَ﴾

ባዩዋቸውም ጊዜ «እነዚህ በእርግጥ ተሳሳቾች ናቸው» ይሉ ነበር፡፡

﴿وَمَا أُرْسِلُوا عَلَيْهِمْ حَافِظِينَ﴾

በነርሱ ላይ ተጠባባቂዎች ተደርገው ያልተላኩ ሲኾኑ፡፡

﴿فَالْيَوْمَ الَّذِينَ آمَنُوا مِنَ الْكُفَّارِ يَضْحَكُونَ﴾

ዛሬ (በትንሣኤ ቀን) እነዚያ ያመኑት በከሓዲዎቹ ይስቃሉ፡፡

﴿عَلَى الْأَرَائِكِ يَنْظُرُونَ﴾

በባለ አጎበር አልጋዎች ላይ ኾነው የሚመለከቱ ሲኾኑ (ይስቃሉ)፡፡

﴿هَلْ ثُوِّبَ الْكُفَّارُ مَا كَانُوا يَفْعَلُونَ﴾

ከሓዲዎች ይሠሩት የነበሩትን (ዋጋ) ተመነዱን? (ይላሉ)፡፡

الترجمات والتفاسير لهذه السورة: