الفجر

تفسير سورة الفجر

الترجمة الأمهرية

አማርኛ

الترجمة الأمهرية

ترجمة معاني القرآن الكريم للغة الامهرية ترجمها الشيخ محمد صادق ومحمد الثاني حبيب . الطبعة 2011م. ملاحظة: ترجمات بعض الآيات (مشار إليها) تم تصويبها بمعرفة مركز رواد الترجمة، مع إتاحة الاطلاع على الترجمة الأصلية لغرض إبداء الرأي والتقييم والتطوير المستمر.

﴿بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَٰنِ الرَّحِيمِ وَالْفَجْرِ﴾

በጎህ እምላለሁ፡፡

﴿وَلَيَالٍ عَشْرٍ﴾

በዐሥር ሌሊቶችም፡፡

﴿وَالشَّفْعِ وَالْوَتْرِ﴾

በጥንዱም በነጠላውም፡፡

﴿وَاللَّيْلِ إِذَا يَسْرِ﴾

በሌሊቱም በሚኼድ ጊዜ፡፡

﴿هَلْ فِي ذَٰلِكَ قَسَمٌ لِذِي حِجْرٍ﴾

በዚህ (መሓላ) ለባለ አእምሮ ታላቅ መሓላ አለበትን?

﴿أَلَمْ تَرَ كَيْفَ فَعَلَ رَبُّكَ بِعَادٍ﴾

ጌታህ በዓድ እንዴት እንደ ሠራ አታውቅምን?

﴿إِرَمَ ذَاتِ الْعِمَادِ﴾

በኢረም በባለ ረዣዢሚቱ አዕማድ፡፡

﴿الَّتِي لَمْ يُخْلَقْ مِثْلُهَا فِي الْبِلَادِ﴾

በዚያች ብጤዋ በአገሮች ውስጥ ያልተፈጠረ በኾነችው፡፡

﴿وَثَمُودَ الَّذِينَ جَابُوا الصَّخْرَ بِالْوَادِ﴾

በሰሙድም በእነዚያ በሸለቆው ቋጥኝን የቆረጡ በኾኑት፡፡

﴿وَفِرْعَوْنَ ذِي الْأَوْتَادِ﴾

በፈርዖንም ባለ ችካሎች በኾነው፡፡

﴿الَّذِينَ طَغَوْا فِي الْبِلَادِ﴾

በእነዚያ በአገሮች ላይ ግፍ የሠሩ፡፡

﴿فَأَكْثَرُوا فِيهَا الْفَسَادَ﴾

በእርሷም ውስጥ ጥፋትን ያበዙ በኾኑት (እንዴት እንደሠራ አታውቅምን?)

﴿فَصَبَّ عَلَيْهِمْ رَبُّكَ سَوْطَ عَذَابٍ﴾

በእነርሱ ላይም ጌታህ የቅጣትን አለንጋ አወረደባቸው፡፡

﴿إِنَّ رَبَّكَ لَبِالْمِرْصَادِ﴾

ጌታህ በመጠባበቂያ ላይ ነውና፡፡

﴿فَأَمَّا الْإِنْسَانُ إِذَا مَا ابْتَلَاهُ رَبُّهُ فَأَكْرَمَهُ وَنَعَّمَهُ فَيَقُولُ رَبِّي أَكْرَمَنِ﴾

ሰውማ ጌታው በሞከረው ጊዜ፣ ባከበረውና ባጣቀመውም (ጊዜ) «ጌታዬ አከበረኝ (አበለጠኝ)» ይላል፡፡

﴿وَأَمَّا إِذَا مَا ابْتَلَاهُ فَقَدَرَ عَلَيْهِ رِزْقَهُ فَيَقُولُ رَبِّي أَهَانَنِ﴾

በሞከረውና በእርሱ ላይ ሲሳዩን ባጠበበ ጊዜማ «ጌታዬ አሳነሰኝ» ይላል፡፡

﴿كَلَّا ۖ بَلْ لَا تُكْرِمُونَ الْيَتِيمَ﴾

ይከልከል፤ ይልቁንም የቲምን አታከብሩም፡፡

﴿وَلَا تَحَاضُّونَ عَلَىٰ طَعَامِ الْمِسْكِينِ﴾

ድኻንም በማብላት ላይ አትታዘዙም፡፡

﴿وَتَأْكُلُونَ التُّرَاثَ أَكْلًا لَمًّا﴾

የውርስንም ገንዘብ የመሰብሰብን አበላል ትበላላችሁ፡፡

﴿وَتُحِبُّونَ الْمَالَ حُبًّا جَمًّا﴾

ገንዘብንም ብዙን መውደድ ትወዳላችሁ፡፡

﴿كَلَّا إِذَا دُكَّتِ الْأَرْضُ دَكًّا دَكًّا﴾

ተዉ፤ ምድር ደጋግማ በተሰባበረች ጊዜ፤

﴿وَجَاءَ رَبُّكَ وَالْمَلَكُ صَفًّا صَفًّا﴾

መላእክትም ሰልፍ ሰልፍ ኾነው ጌታህ (ለሱ ክብር በምስማማ መልኩ) በመጣ ጊዜ፤

﴿وَجِيءَ يَوْمَئِذٍ بِجَهَنَّمَ ۚ يَوْمَئِذٍ يَتَذَكَّرُ الْإِنْسَانُ وَأَنَّىٰ لَهُ الذِّكْرَىٰ﴾

ገሀነምም በዚያ ቀን በተመጣች ጊዜ በዚያ ቀን ሰው (ጥፋቱን) ይገነዘባል፡፡ መገንዘብም ለእርሱ ከየቱ?

﴿يَقُولُ يَا لَيْتَنِي قَدَّمْتُ لِحَيَاتِي﴾

«ዋ እኔ! ምነው በሕይወቴ (መልካምን ሥራ) ባስቀደምኩ ኖሮ» ይላል፡፡

﴿فَيَوْمَئِذٍ لَا يُعَذِّبُ عَذَابَهُ أَحَدٌ﴾

በዚያ ቀንም የርሱን አቀጣጥ አንድም አይቀጣም፡፡

﴿وَلَا يُوثِقُ وَثَاقَهُ أَحَدٌ﴾

የእርሱንም አስተሳሰር አንድም አያስርም፡፡

﴿يَا أَيَّتُهَا النَّفْسُ الْمُطْمَئِنَّةُ﴾

(ለአመነች ነፍስም) «አንቺ የረካሺው ነፍስ ሆይ!

﴿ارْجِعِي إِلَىٰ رَبِّكِ رَاضِيَةً مَرْضِيَّةً﴾

«ወዳጅ ተወዳጅ ኾነሽ ወደ ጌታሽ ተመለሺ፡፡

﴿فَادْخُلِي فِي عِبَادِي﴾

«በባሮቼም ውስጥ ግቢ፡፡

﴿وَادْخُلِي جَنَّتِي﴾

ገነቴንም ግቢ፤» (ትባላለች)፡፡

الترجمات والتفاسير لهذه السورة: