الإنشقاق

تفسير سورة الإنشقاق

الترجمة الأمهرية

አማርኛ

الترجمة الأمهرية

ترجمة معاني القرآن الكريم للغة الامهرية ترجمها الشيخ محمد صادق ومحمد الثاني حبيب . الطبعة 2011م. ملاحظة: ترجمات بعض الآيات (مشار إليها) تم تصويبها بمعرفة مركز رواد الترجمة، مع إتاحة الاطلاع على الترجمة الأصلية لغرض إبداء الرأي والتقييم والتطوير المستمر.

﴿بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَٰنِ الرَّحِيمِ إِذَا السَّمَاءُ انْشَقَّتْ﴾

ሰማይ በተቀደደች ጊዜ፤

﴿وَأَذِنَتْ لِرَبِّهَا وَحُقَّتْ﴾

ለጌታዋም (ትዕዛዝ) በሰማች ጊዜ፤ (ልትሰማ) ተገባትም፤

﴿وَإِذَا الْأَرْضُ مُدَّتْ﴾

ምድርም በተለጠጠች ጊዜ፤

﴿وَأَلْقَتْ مَا فِيهَا وَتَخَلَّتْ﴾

በውስጧ ያለውንም ሁሉ በጣለችና ባዶ በኾነች ጊዜ፤

﴿وَأَذِنَتْ لِرَبِّهَا وَحُقَّتْ﴾

ለጌታዋም በሰማች ጊዜ፤ (መስማት) ተገባትም፤ (ሰው ሁሉ ሥራውን ይገናኛል)፡፡

﴿يَا أَيُّهَا الْإِنْسَانُ إِنَّكَ كَادِحٌ إِلَىٰ رَبِّكَ كَدْحًا فَمُلَاقِيهِ﴾

አንተ ሰው ሆይ! አንተ ጌታህን (በሞት) እስከምትገናኝ ድረስ ልፋትን ለፊ ነህ፤ ተገናኚውም ነህ፡፡

﴿فَأَمَّا مَنْ أُوتِيَ كِتَابَهُ بِيَمِينِهِ﴾

መጽሐፉን በቀኙ የተሰጠ ሰውማ፤

﴿فَسَوْفَ يُحَاسَبُ حِسَابًا يَسِيرًا﴾

በእርግጥ ቀላልን ምርመራ ይመረመራል፡፡

﴿وَيَنْقَلِبُ إِلَىٰ أَهْلِهِ مَسْرُورًا﴾

ወደ ቤተሰቦቹም ተደሳች ኾኖ ይመለሳል፡፡

﴿وَأَمَّا مَنْ أُوتِيَ كِتَابَهُ وَرَاءَ ظَهْرِهِ﴾

መጽሐፉን በጀርባው ኋላ የተሰጠ ሰውማ፤

﴿فَسَوْفَ يَدْعُو ثُبُورًا﴾

(ዋ! ጥፋቴ በማለት) ጥፋትን በእርግጥ ይጠራል፡፡

﴿وَيَصْلَىٰ سَعِيرًا﴾

የተጋጋመች እሳትንም ይገባል፡፡

﴿إِنَّهُ كَانَ فِي أَهْلِهِ مَسْرُورًا﴾

እርሱ በቤተሰቡ ውስጥ ተደሳች ነበርና፡፡

﴿إِنَّهُ ظَنَّ أَنْ لَنْ يَحُورَ﴾

እርሱ (ወደ አላህ) የማይመለስ መኾኑን አስቧልና፡፡

﴿بَلَىٰ إِنَّ رَبَّهُ كَانَ بِهِ بَصِيرًا﴾

አይደለም (ይመለሳል)፡፡ ጌታው በእርሱ (መመለስ) ዐዋቂ ነበር፤ (ነውም)፡፡

﴿فَلَا أُقْسِمُ بِالشَّفَقِ﴾

አትካዱ፤ በወጋገኑ እምላለሁ፡፡

﴿وَاللَّيْلِ وَمَا وَسَقَ﴾

በሌሊቱም በሰበሰውም ሁሉ፤

﴿وَالْقَمَرِ إِذَا اتَّسَقَ﴾

በጨረቃውም በሞላ ጊዜ (እምላለሁ)፡፡

﴿لَتَرْكَبُنَّ طَبَقًا عَنْ طَبَقٍ﴾

ከኹነታ በኋላ ወደ ሌላ ኹነታ ትለዋወጣላችሁ፡፡

﴿فَمَا لَهُمْ لَا يُؤْمِنُونَ﴾

የማያምኑት ለእነርሱ ምን አላቸው?

﴿وَإِذَا قُرِئَ عَلَيْهِمُ الْقُرْآنُ لَا يَسْجُدُونَ ۩﴾

በእነርሱም ላይ ቁርኣን በተነበበ ጊዜ የማይሰግዱት፤ (ምንአላቸው?)

﴿بَلِ الَّذِينَ كَفَرُوا يُكَذِّبُونَ﴾

በእርግጡ እነዚያ የካዱት (በትንሣኤ) ያስተባብላሉ፡፡

﴿وَاللَّهُ أَعْلَمُ بِمَا يُوعُونَ﴾

አላህም (በልቦቻቸው) የሚቆጥሩትን ዐዋቂ ነው፡፡

﴿فَبَشِّرْهُمْ بِعَذَابٍ أَلِيمٍ﴾

በአሳማሚ ቅጣትም አብስራቸው፡፡

﴿إِلَّا الَّذِينَ آمَنُوا وَعَمِلُوا الصَّالِحَاتِ لَهُمْ أَجْرٌ غَيْرُ مَمْنُونٍ﴾

ግን እነዚያ ያመኑና መልካሞችን የሠሩ ለእነርሱ የማይቆረጥ ምንዳ አልላቸው፡፡

الترجمات والتفاسير لهذه السورة: