النبأ

تفسير سورة النبأ

الترجمة الأمهرية

አማርኛ

الترجمة الأمهرية

ترجمة معاني القرآن الكريم للغة الامهرية ترجمها الشيخ محمد صادق ومحمد الثاني حبيب . الطبعة 2011م. ملاحظة: ترجمات بعض الآيات (مشار إليها) تم تصويبها بمعرفة مركز رواد الترجمة، مع إتاحة الاطلاع على الترجمة الأصلية لغرض إبداء الرأي والتقييم والتطوير المستمر.

﴿بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَٰنِ الرَّحِيمِ عَمَّ يَتَسَاءَلُونَ﴾

ከምን ነገር ይጠያየቃሉ?

﴿عَنِ النَّبَإِ الْعَظِيمِ﴾

ከታላቁ ዜና (ከቁርኣን ይጠያየቃሉ)፡፡

﴿الَّذِي هُمْ فِيهِ مُخْتَلِفُونَ﴾

ከዚያ እነርሱ በእርሱ የተለያዩበት ከኾነው፡፡

﴿كَلَّا سَيَعْلَمُونَ﴾

ይከልከሉ፤ ወደፊት (የሚደርስበቸውን) በእርግጥ ያውቃሉ፡፡

﴿ثُمَّ كَلَّا سَيَعْلَمُونَ﴾

ከዚያም ይከልከሉ፤ ወደፊት ያውቃሉ፡፡

﴿أَلَمْ نَجْعَلِ الْأَرْضَ مِهَادًا﴾

ምድርን ምንጣፍ አላደረግንምን?

﴿وَالْجِبَالَ أَوْتَادًا﴾

ጋራዎችንም ችካሎች አላደረግንምን?

﴿وَخَلَقْنَاكُمْ أَزْوَاجًا﴾

ብዙ ዓይነቶችም አድርገን ፈጠርናችሁ፡፡

﴿وَجَعَلْنَا نَوْمَكُمْ سُبَاتًا﴾

እንቅልፋችሁንም ዕረፍት አደረግን፡፡

﴿وَجَعَلْنَا اللَّيْلَ لِبَاسًا﴾

ሌሊቱንም ልባስ አደረግን፡፡

﴿وَجَعَلْنَا النَّهَارَ مَعَاشًا﴾

ቀኑንም (ለኑሮ) መስሪያ አደረግን፡፡

﴿وَبَنَيْنَا فَوْقَكُمْ سَبْعًا شِدَادًا﴾

ከበላያችሁም ሰባትን ብርቱዎች (ሰማያት) ገነባን፡፡

﴿وَجَعَلْنَا سِرَاجًا وَهَّاجًا﴾

አንጸባራቂ ብርሃንንም አደረግን፡፡

﴿وَأَنْزَلْنَا مِنَ الْمُعْصِرَاتِ مَاءً ثَجَّاجًا﴾

ከአረገዙት ደመናዎችም ተንቧቢ ውሃን አወረድን፡፡

﴿لِنُخْرِجَ بِهِ حَبًّا وَنَبَاتًا﴾

በእርሱ እኽልንና ቅጠላ ቅጠልን እናወጣ ዘንድ (አወረድን)፡፡

﴿وَجَنَّاتٍ أَلْفَافًا﴾

የተቆላለፉ አትክልቶችንም፡፡

﴿إِنَّ يَوْمَ الْفَصْلِ كَانَ مِيقَاتًا﴾

የመለያው ቀን የተወሰነ ጊዜ ነው፡፡

﴿يَوْمَ يُنْفَخُ فِي الصُّورِ فَتَأْتُونَ أَفْوَاجًا﴾

በቀንዱ በሚነፋና የተለያዩ ጭፍሮች ኾናችሁ በምትመጡ ቀን ነው፡፡

﴿وَفُتِحَتِ السَّمَاءُ فَكَانَتْ أَبْوَابًا﴾

ሰማይም በምትከፈትና (ባለ) ደጃፎችም በምትኾንበት፡፡

﴿وَسُيِّرَتِ الْجِبَالُ فَكَانَتْ سَرَابًا﴾

ጋራዎችም በሚነዱበት (እንደ) ሲሪብዱም በሚኾኑበት (ቀን) ነው፡፡

﴿إِنَّ جَهَنَّمَ كَانَتْ مِرْصَادًا﴾

ገሀነም መጠባበቂያ (ስፍራ) ናት፡፡

﴿لِلطَّاغِينَ مَآبًا﴾

ለሕግ ተላላፊዎች መመለሻ ስትኾን፡፡

﴿لَابِثِينَ فِيهَا أَحْقَابًا﴾

በውስጧ ብዙን ዘመናት ነዋሪዎች ሲኾኑ፤

﴿لَا يَذُوقُونَ فِيهَا بَرْدًا وَلَا شَرَابًا﴾

በውስጧ ቅዝቃዜንም መጠጥንም አይቀምሱም፡፡

﴿إِلَّا حَمِيمًا وَغَسَّاقًا﴾

ግን ሙቅ ውሃንና እዥን (ይቀምሳሉ)፡፡

﴿جَزَاءً وِفَاقًا﴾

ተስማሚን ምንዳ ይምመነዳሉ፡፡

﴿إِنَّهُمْ كَانُوا لَا يَرْجُونَ حِسَابًا﴾

እነርሱ ምርመራን የማይፈሩ ነበሩና፡፡

﴿وَكَذَّبُوا بِآيَاتِنَا كِذَّابًا﴾

በአንቀጾቻችንም ማስተባበልን አስተባበሉና፡፡

﴿وَكُلَّ شَيْءٍ أَحْصَيْنَاهُ كِتَابًا﴾

ነገሩንም ሁሉ የተጻፈ ሲኾን አጠቃለልነው፡፡

﴿فَذُوقُوا فَلَنْ نَزِيدَكُمْ إِلَّا عَذَابًا﴾

ቅመሱም ቅጣትንም እንጅ (ሌላን) አንጨምራችሁም (ይባላሉ)፡፡

﴿إِنَّ لِلْمُتَّقِينَ مَفَازًا﴾

ለጥንቁቆቹ መዳኛ ስፍራ አልላቸው፡፡

﴿حَدَائِقَ وَأَعْنَابًا﴾

አትክልቶችና ወይኖችም፡፡

﴿وَكَوَاعِبَ أَتْرَابًا﴾

እኩያዎች የኾኑ ጡተ ጉቻማዎችም፡፡

﴿وَكَأْسًا دِهَاقًا﴾

የተሞሉ ብርጭቆዎችም፡፡

﴿لَا يَسْمَعُونَ فِيهَا لَغْوًا وَلَا كِذَّابًا﴾

በውስጧ ትርፍ ቃልንም ማስዋሸትንም አይሰሙም፡፡

﴿جَزَاءً مِنْ رَبِّكَ عَطَاءً حِسَابًا﴾

ከጌታህ የኾነን ምንዳ በቂ ስጦታን (ተሰጡ)፡፡

﴿رَبِّ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ وَمَا بَيْنَهُمَا الرَّحْمَٰنِ ۖ لَا يَمْلِكُونَ مِنْهُ خِطَابًا﴾

የሰማያትና የምድር በመካከላቸውም ያለው ሁሉ ጌታ በጣም አዛኝ ከኾነው (ተመነዱ)፡፡ ከእርሱ ጋር መነጋገርን አይችሉም፡፡

﴿يَوْمَ يَقُومُ الرُّوحُ وَالْمَلَائِكَةُ صَفًّا ۖ لَا يَتَكَلَّمُونَ إِلَّا مَنْ أَذِنَ لَهُ الرَّحْمَٰنُ وَقَالَ صَوَابًا﴾

መንፈሱ (ጂብሪል) መላእክቶቹም የተሰለፉ ኾነው በሚቆሙ ቀን አል-ረሕማን ለእርሱ የፈቀደለትና ትክክለኛን ቃል ያለ ሰው ቢኾን እንጅ (መነጋገርን አይችሉም)፡፡

﴿ذَٰلِكَ الْيَوْمُ الْحَقُّ ۖ فَمَنْ شَاءَ اتَّخَذَ إِلَىٰ رَبِّهِ مَآبًا﴾

ይህ የተረጋገጠው ቀን ነው፡፡ የሻም ሰው ወደ ጌታው መመለስን ይይዛል፡፡

﴿إِنَّا أَنْذَرْنَاكُمْ عَذَابًا قَرِيبًا يَوْمَ يَنْظُرُ الْمَرْءُ مَا قَدَّمَتْ يَدَاهُ وَيَقُولُ الْكَافِرُ يَا لَيْتَنِي كُنْتُ تُرَابًا﴾

እኛ ሰው ሁሉ እጆቹ ያስቀደሙትን በሚያይበትና ከሓዲውም ዋ ምኞቴ! ምንነው ዐፈር በኾንኩ በሚልበት ቀን ቅርብ የኾነን ቅጣት አስጠነቀቅናችሁ፡፡

الترجمات والتفاسير لهذه السورة: