الإنفطار

تفسير سورة الإنفطار

الترجمة الأمهرية

አማርኛ

الترجمة الأمهرية

ترجمة معاني القرآن الكريم للغة الامهرية ترجمها الشيخ محمد صادق ومحمد الثاني حبيب . الطبعة 2011م. ملاحظة: ترجمات بعض الآيات (مشار إليها) تم تصويبها بمعرفة مركز رواد الترجمة، مع إتاحة الاطلاع على الترجمة الأصلية لغرض إبداء الرأي والتقييم والتطوير المستمر.

﴿بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَٰنِ الرَّحِيمِ إِذَا السَّمَاءُ انْفَطَرَتْ﴾

ሰማይ በተሰነጠቀች ጊዜ፤

﴿وَإِذَا الْكَوَاكِبُ انْتَثَرَتْ﴾

ከዋክብትም ተበታትነው በወደቁ ጊዜ፤

﴿وَإِذَا الْبِحَارُ فُجِّرَتْ﴾

ባሕሮችም በተከፈቱና በተደበላለቁ ጊዜ፤

﴿وَإِذَا الْقُبُورُ بُعْثِرَتْ﴾

መቃብሮችም በተገለባበጡና (ሙታን) በተነሱ ጊዜ፤

﴿عَلِمَتْ نَفْسٌ مَا قَدَّمَتْ وَأَخَّرَتْ﴾

ማንኛይቱም ነፍስ ያስቀደመችውንና ያቆየችውን ታውቃለች፡፡

﴿يَا أَيُّهَا الْإِنْسَانُ مَا غَرَّكَ بِرَبِّكَ الْكَرِيمِ﴾

አንተ ሰው ሆይ! በቸሩ ጌታህ ምን አታለለህ?

﴿الَّذِي خَلَقَكَ فَسَوَّاكَ فَعَدَلَكَ﴾

በዚያ በፈጠረህ አካለ ሙሉም ባደረገህ ባስተካከለህም፡፡

﴿فِي أَيِّ صُورَةٍ مَا شَاءَ رَكَّبَكَ﴾

በማንኛውም በሻው ቅርፅ በገጣጠመህ (ጌታህ ምን አታለለህ)፡፡

﴿كَلَّا بَلْ تُكَذِّبُونَ بِالدِّينِ﴾

ተከልከሉ፤ በእውነቱ በፍርዱ ቀን ታስተባብላላችሁ፡፡

﴿وَإِنَّ عَلَيْكُمْ لَحَافِظِينَ﴾

በእናንተ ላይ ተጠባባቂዎች ያሉባችሁ፤ ስትኾኑ፤

﴿كِرَامًا كَاتِبِينَ﴾

የተከበሩ ጸሐፊዎች የኾኑ፤ (ተጠባባቂዎች)፡፡

﴿يَعْلَمُونَ مَا تَفْعَلُونَ﴾

የምትሠሩትን ሁሉ የሚያውቁ፡፡

﴿إِنَّ الْأَبْرَارَ لَفِي نَعِيمٍ﴾

እውነተኞቹ ምእምናን በእርግጥ በገነት ውስጥ ናቸው፡፡

﴿وَإِنَّ الْفُجَّارَ لَفِي جَحِيمٍ﴾

ከሓዲዎቹም በእርግጥ በገሀነም ውስጥ ናቸው፡፡

﴿يَصْلَوْنَهَا يَوْمَ الدِّينِ﴾

በፍርዱ ቀን ይገቧታል፡፡

﴿وَمَا هُمْ عَنْهَا بِغَائِبِينَ﴾

እነርሱም ከርሷ ራቂዎች አይደሉም፡፡

﴿وَمَا أَدْرَاكَ مَا يَوْمُ الدِّينِ﴾

የፍርድ ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?

﴿ثُمَّ مَا أَدْرَاكَ مَا يَوْمُ الدِّينِ﴾

ከዚያም የፍርዱ ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?

﴿يَوْمَ لَا تَمْلِكُ نَفْسٌ لِنَفْسٍ شَيْئًا ۖ وَالْأَمْرُ يَوْمَئِذٍ لِلَّهِ﴾

(እርሱ) ማንኛይቱም ነፍስ ለሌላይቱ ነፍስ ምንም ማድረግን የማትችልበት ቀን ነው፡፡ ነገሩም ሁሉ በዚያ ቀን ለአላህ ብቻ ነው፡፡

الترجمات والتفاسير لهذه السورة: