الليل

تفسير سورة الليل

الترجمة الأمهرية

አማርኛ

الترجمة الأمهرية

ترجمة معاني القرآن الكريم للغة الامهرية ترجمها الشيخ محمد صادق ومحمد الثاني حبيب . الطبعة 2011م. ملاحظة: ترجمات بعض الآيات (مشار إليها) تم تصويبها بمعرفة مركز رواد الترجمة، مع إتاحة الاطلاع على الترجمة الأصلية لغرض إبداء الرأي والتقييم والتطوير المستمر.

﴿بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَٰنِ الرَّحِيمِ وَاللَّيْلِ إِذَا يَغْشَىٰ﴾

በሌሊቱ እምላለሁ (በጨለማው) በሚሸፍን ጊዜ፡፡

﴿وَالنَّهَارِ إِذَا تَجَلَّىٰ﴾

በቀኑም፤ በተገለጸ ጊዜ፡፡

﴿وَمَا خَلَقَ الذَّكَرَ وَالْأُنْثَىٰ﴾

ወንድንና ሴትን በፈጠረውም (አምላክ እምላለሁ)፡፡

﴿إِنَّ سَعْيَكُمْ لَشَتَّىٰ﴾

ሥራችሁ በእርግጥ የተለያየ ነው፡፡

﴿فَأَمَّا مَنْ أَعْطَىٰ وَاتَّقَىٰ﴾

የሰጠ ሰውማ ጌታውን የፈራም፡፡

﴿وَصَدَّقَ بِالْحُسْنَىٰ﴾

በመልካሚቱም (እምነት) ያረጋገጠ፤

﴿فَسَنُيَسِّرُهُ لِلْيُسْرَىٰ﴾

ለገሪቱ ሥራ እናዘጋጀዋለን፡፡

﴿وَأَمَّا مَنْ بَخِلَ وَاسْتَغْنَىٰ﴾

የሰሰተ ሰውማ የተብቃቃም፤ (በራሱ የተመካ)፤

﴿وَكَذَّبَ بِالْحُسْنَىٰ﴾

በመልካሚቱ (እምነት) ያሰተባበለም፤

﴿فَسَنُيَسِّرُهُ لِلْعُسْرَىٰ﴾

ለክፉይቱ ሥራ እናዘጋጀዋለን፡፡

﴿وَمَا يُغْنِي عَنْهُ مَالُهُ إِذَا تَرَدَّىٰ﴾

በወደቀም ጊዜ ገንዘቡ ከእርሱ ምንም አይጠቅመውም፡፡

﴿إِنَّ عَلَيْنَا لَلْهُدَىٰ﴾

ቅኑን መንገድ መግለጽ በእኛ ላይ አለብን፡፡

﴿وَإِنَّ لَنَا لَلْآخِرَةَ وَالْأُولَىٰ﴾

መጨረሻይቱም መጀመሪያይቱም ዓለም የእኛ ናቸው፡፡

﴿فَأَنْذَرْتُكُمْ نَارًا تَلَظَّىٰ﴾

የምትንቀለቀልንም እሳት አስጠነቀቅኳችሁ (በላቸው)፡፡

﴿لَا يَصْلَاهَا إِلَّا الْأَشْقَى﴾

ከጠማማ በቀር ሌላ የማይገባት የኾነችን፡፡

﴿الَّذِي كَذَّبَ وَتَوَلَّىٰ﴾

ያ ያስተባበለና ከትዕዛዝ የሸሸው፡፡

﴿وَسَيُجَنَّبُهَا الْأَتْقَى﴾

አላህን በጣም ፈሪውም በእርግጥ ይርቃታል፡፡

﴿الَّذِي يُؤْتِي مَالَهُ يَتَزَكَّىٰ﴾

ያ የሚጥራራ ኾኖ ገንዘቡን (ለድኾች) የሚሰጠው፡፡

﴿وَمَا لِأَحَدٍ عِنْدَهُ مِنْ نِعْمَةٍ تُجْزَىٰ﴾

ለአንድም ሰው እርሱ ዘንድ የምትመለስ ውለታ የለችም፡፡

﴿إِلَّا ابْتِغَاءَ وَجْهِ رَبِّهِ الْأَعْلَىٰ﴾

ግን የታላቅ ጌታውን ውዴታ ለመፈለግ (ይህንን ሠራ)፡፡

﴿وَلَسَوْفَ يَرْضَىٰ﴾

ወደፊትም በእርግጥ ይደሰታል፡፡

الترجمات والتفاسير لهذه السورة: