الأعلى

تفسير سورة الأعلى

الترجمة الأمهرية

አማርኛ

الترجمة الأمهرية

ترجمة معاني القرآن الكريم للغة الامهرية ترجمها الشيخ محمد صادق ومحمد الثاني حبيب . الطبعة 2011م. ملاحظة: ترجمات بعض الآيات (مشار إليها) تم تصويبها بمعرفة مركز رواد الترجمة، مع إتاحة الاطلاع على الترجمة الأصلية لغرض إبداء الرأي والتقييم والتطوير المستمر.

﴿بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَٰنِ الرَّحِيمِ سَبِّحِ اسْمَ رَبِّكَ الْأَعْلَى﴾

ከሁሉ በላይ የኾነውን ጌታህን ስም አሞግሥ፡፡

﴿الَّذِي خَلَقَ فَسَوَّىٰ﴾

የዚያን (ሁሉን ነገር) የፈጠረውን ያስተካከለውንም፡፡

﴿وَالَّذِي قَدَّرَ فَهَدَىٰ﴾

የዚያንም የወሰነውን፡፡ (ለተፈጠረለት ነገር) የመራውንም፡፡

﴿وَالَّذِي أَخْرَجَ الْمَرْعَىٰ﴾

የዚያንም ግጦሽን (ለምለም አድርጎ) ያወጣውን፡፡

﴿فَجَعَلَهُ غُثَاءً أَحْوَىٰ﴾

(ከዚያ) ደረቅ ጥቁር ያደረገውንም (አምላክ ስም አሞግስ)፡፡

﴿سَنُقْرِئُكَ فَلَا تَنْسَىٰ﴾

(ቁርኣንን) በእርግጥ እናስነብብሃለን፤ አትረሳምም፡፡

﴿إِلَّا مَا شَاءَ اللَّهُ ۚ إِنَّهُ يَعْلَمُ الْجَهْرَ وَمَا يَخْفَىٰ﴾

አላህ ከሻው ነገር በስተቀር፡፡ እርሱ ግልጹን የሚሸሸገውንም ሁሉ ያውቃልና፡፡

﴿وَنُيَسِّرُكَ لِلْيُسْرَىٰ﴾

ለገሪቱም (ሕግጋት) እንገጥምሃለን፡፡

﴿فَذَكِّرْ إِنْ نَفَعَتِ الذِّكْرَىٰ﴾

ግሣጼይቱ ብትጠቅም (ሰዎችን) ገሥጽም፡፡

﴿سَيَذَّكَّرُ مَنْ يَخْشَىٰ﴾

(አላህን) የሚፈራ ሰው በእርግጥ ይገሠጻል፡፡

﴿وَيَتَجَنَّبُهَا الْأَشْقَى﴾

መናጢውም ይርቃታል፡፡

﴿الَّذِي يَصْلَى النَّارَ الْكُبْرَىٰ﴾

ያ ታላቂቱን እሳት የሚገባው፡፡

﴿ثُمَّ لَا يَمُوتُ فِيهَا وَلَا يَحْيَىٰ﴾

ከዚያም በእርሷ ውስጥ አይሞትም ሕያውም አይኾንም፡፡

﴿قَدْ أَفْلَحَ مَنْ تَزَكَّىٰ﴾

የተጥራራ ሰው በእርግጥ ዳነ፡፡

﴿وَذَكَرَ اسْمَ رَبِّهِ فَصَلَّىٰ﴾

የጌታውንም ስም ያወሳና የሰገደ፡፡

﴿بَلْ تُؤْثِرُونَ الْحَيَاةَ الدُّنْيَا﴾

ይልቁንም ቅርቢቱን ሕይወት ትመርጣላችሁ፡፡

﴿وَالْآخِرَةُ خَيْرٌ وَأَبْقَىٰ﴾

መጨረሻይቱ (ሕይወት) በላጭ ሁል ጊዜ ዘውታሪም ስትኾን፡፡

﴿إِنَّ هَٰذَا لَفِي الصُّحُفِ الْأُولَىٰ﴾

ይህ በፊተኞቹ መጻሕፍት ውስጥ ያልለ ነው፡፡

﴿صُحُفِ إِبْرَاهِيمَ وَمُوسَىٰ﴾

በኢብራሂምና በሙሳ ጽሑፎች ውስጥ፡፡

الترجمات والتفاسير لهذه السورة: