الغاشية

تفسير سورة الغاشية

الترجمة الأمهرية

አማርኛ

الترجمة الأمهرية

ترجمة معاني القرآن الكريم للغة الامهرية ترجمها الشيخ محمد صادق ومحمد الثاني حبيب . الطبعة 2011م. ملاحظة: ترجمات بعض الآيات (مشار إليها) تم تصويبها بمعرفة مركز رواد الترجمة، مع إتاحة الاطلاع على الترجمة الأصلية لغرض إبداء الرأي والتقييم والتطوير المستمر.

﴿بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَٰنِ الرَّحِيمِ هَلْ أَتَاكَ حَدِيثُ الْغَاشِيَةِ﴾

የሸፋኝቱ (ትንሣኤ) ወሬ መጣህን?

﴿وُجُوهٌ يَوْمَئِذٍ خَاشِعَةٌ﴾

ፊቶች በዚያ ቀን ተዋራጆች ናቸው፡፡

﴿عَامِلَةٌ نَاصِبَةٌ﴾

ሠሪዎች ለፊዎች ናቸው፡፡

﴿تَصْلَىٰ نَارًا حَامِيَةً﴾

ተኳሳን እሳት ይገባሉ፡፡

﴿تُسْقَىٰ مِنْ عَيْنٍ آنِيَةٍ﴾

በጣም ከፈላች ምንጭ ይጋታሉ፡፡

﴿لَيْسَ لَهُمْ طَعَامٌ إِلَّا مِنْ ضَرِيعٍ﴾

ለእነርሱ ዶሪዕ ከሚባል (እሾሃም) ዛፍ እንጅ ሌላ ምግብ የላቸውም፡፡

﴿لَا يُسْمِنُ وَلَا يُغْنِي مِنْ جُوعٍ﴾

የማያሰባ ከረኃብም የማያብቃቃ ከኾነው፡፡

﴿وُجُوهٌ يَوْمَئِذٍ نَاعِمَةٌ﴾

ፊቶች በዚያ ቀን ተቀማጣዮች ናቸው፡፡

﴿لِسَعْيِهَا رَاضِيَةٌ﴾

ለሥራቸው ተደሳቾች ናቸው፡፡

﴿فِي جَنَّةٍ عَالِيَةٍ﴾

በከፍተኛ ገነት ውስጥ ናቸው፡፡

﴿لَا تَسْمَعُ فِيهَا لَاغِيَةً﴾

በውስጧ ውድቅን ነገር አይሰሙም፡፡

﴿فِيهَا عَيْنٌ جَارِيَةٌ﴾

በውስጧ ፈሳሾች ምንጮች አልሉ፡፡

﴿فِيهَا سُرُرٌ مَرْفُوعَةٌ﴾

በውስጧ ከፍ የተደረጉ አልጋዎች አልሉ፡፡

﴿وَأَكْوَابٌ مَوْضُوعَةٌ﴾

በተርታ የተኖሩ ብርጭቆዎችም፡፡

﴿وَنَمَارِقُ مَصْفُوفَةٌ﴾

የተደረደሩ መከዳዎችም፡፡

﴿وَزَرَابِيُّ مَبْثُوثَةٌ﴾

የተነጠፉ ስጋጃዎችም (አልሉ)፡፡

﴿أَفَلَا يَنْظُرُونَ إِلَى الْإِبِلِ كَيْفَ خُلِقَتْ﴾

(ከሓዲዎች) አይመለከቱምን? ወደ ግመል እንዴት እነደተፈጠረች!

﴿وَإِلَى السَّمَاءِ كَيْفَ رُفِعَتْ﴾

ወደ ሰማይም እንዴት ከፍ እንደ ተደረገች!

﴿وَإِلَى الْجِبَالِ كَيْفَ نُصِبَتْ﴾

ወደ ተራራዎችም እንዴት እንደ ተቸከሉ!

﴿وَإِلَى الْأَرْضِ كَيْفَ سُطِحَتْ﴾

ወደ ምድርም እንዴ እንደተዘረጋች (አይመለከቱምን?)

﴿فَذَكِّرْ إِنَّمَا أَنْتَ مُذَكِّرٌ﴾

አስታውስም፤ አንተ አስታዋሽ ብቻ ነህና፡፡

﴿لَسْتَ عَلَيْهِمْ بِمُصَيْطِرٍ﴾

በእነርሱ ላይ ተሿሚ (አስገዳጅ) አይደለህም፡፡

﴿إِلَّا مَنْ تَوَلَّىٰ وَكَفَرَ﴾

ግን (ከእውነት) የዞረና የካደ ሰው፤

﴿فَيُعَذِّبُهُ اللَّهُ الْعَذَابَ الْأَكْبَرَ﴾

አላህ ታላቁን ቅጣት ይቀጣዋል፡፡

﴿إِنَّ إِلَيْنَا إِيَابَهُمْ﴾

መመለሻቸው ወደእኛ ብቻ ነው፡፡

﴿ثُمَّ إِنَّ عَلَيْنَا حِسَابَهُمْ﴾

ከዚያም ምርመራቸው በእኛ ላይ ብቻ ነው፡፡

الترجمات والتفاسير لهذه السورة: