عبس

تفسير سورة عبس

الترجمة الأمهرية

አማርኛ

الترجمة الأمهرية

ترجمة معاني القرآن الكريم للغة الامهرية ترجمها الشيخ محمد صادق ومحمد الثاني حبيب . الطبعة 2011م. ملاحظة: ترجمات بعض الآيات (مشار إليها) تم تصويبها بمعرفة مركز رواد الترجمة، مع إتاحة الاطلاع على الترجمة الأصلية لغرض إبداء الرأي والتقييم والتطوير المستمر.

﴿بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَٰنِ الرَّحِيمِ عَبَسَ وَتَوَلَّىٰ﴾

ፊቱን አጨፈገገ፤ ዞረም፡፡

﴿أَنْ جَاءَهُ الْأَعْمَىٰ﴾

ዕውሩ ስለ መጣው፡፡

﴿وَمَا يُدْرِيكَ لَعَلَّهُ يَزَّكَّىٰ﴾

ምን ያሳውቅሃል? (ከኀጢአቶቹ) ሊጥራራ ይከጀላል፡፡

﴿أَوْ يَذَّكَّرُ فَتَنْفَعَهُ الذِّكْرَىٰ﴾

ወይም ሊገሠጽ ግሠጼይቱም ልትጠቅመው (ይከጀላል)፡፡

﴿أَمَّا مَنِ اسْتَغْنَىٰ﴾

የተብቃቃው ሰውማ፤

﴿فَأَنْتَ لَهُ تَصَدَّىٰ﴾

አንተ ለእርሱ (ለእምነቱ በመጓጓት) በፈገግታ ትቀበለዋለህ፡፡

﴿وَمَا عَلَيْكَ أَلَّا يَزَّكَّىٰ﴾

ባይጥራራ (ባያምን) ባንተ ላይ ምንም የሌለብህ ስትኾን፡፡

﴿وَأَمَّا مَنْ جَاءَكَ يَسْعَىٰ﴾

እየገሰገሰ የመጣህ ሰውማ፤

﴿وَهُوَ يَخْشَىٰ﴾

እርሱ (አላህን) የሚፈራ ሲኾን፤

﴿فَأَنْتَ عَنْهُ تَلَهَّىٰ﴾

አንተ ከእርሱ ትዝዘናጋለህ፡፡

﴿كَلَّا إِنَّهَا تَذْكِرَةٌ﴾

ተከልከል፡፡ እርሷ ማስገንዘቢያ ናት፡፡

﴿فَمَنْ شَاءَ ذَكَرَهُ﴾

የሻም ሰው (ቁርኣኑን) ያስታውሰዋል፡፡

﴿فِي صُحُفٍ مُكَرَّمَةٍ﴾

በተከበሩ ጽሑፎች ውስጥ ነው፡፡

﴿مَرْفُوعَةٍ مُطَهَّرَةٍ﴾

ከፍ በተደረገች ንጹሕ በተደረገች (ጽሑፍ ውስጥ ነው)፡፡

﴿بِأَيْدِي سَفَرَةٍ﴾

በጸሐፊዎቹ (መላእክት) እጆች (ንጹሕ የተደረገች)፡፡

﴿كِرَامٍ بَرَرَةٍ﴾

የተከበሩና ታዛዦች በኾኑት (ጸሐፊዎች እጆች)፡፡

﴿قُتِلَ الْإِنْسَانُ مَا أَكْفَرَهُ﴾

ሰው ተረገመ፤ ምን ከሓዲ አደረገው?

﴿مِنْ أَيِّ شَيْءٍ خَلَقَهُ﴾

(ጌታው) በምን ነገር ፈጠረው? (አያስብምን?)

﴿مِنْ نُطْفَةٍ خَلَقَهُ فَقَدَّرَهُ﴾

ከፍትወት ጠብታ ፈጠረው፤ መጠነውም፡፡

﴿ثُمَّ السَّبِيلَ يَسَّرَهُ﴾

ከዚያም (መውጫ) መንገዱን አገራው፡፡

﴿ثُمَّ أَمَاتَهُ فَأَقْبَرَهُ﴾

ከዚያም ገደለው፤ እንዲቀበርም አደረገው፡፡

﴿ثُمَّ إِذَا شَاءَ أَنْشَرَهُ﴾

ከዚያም (ማንሳቱን) በሻ ጊዜ ያስነሳዋል፡፡

﴿كَلَّا لَمَّا يَقْضِ مَا أَمَرَهُ﴾

በእውነት ያንን (ጌታው) ያዘዘውን ገና አልፈጸመም፡፡

﴿فَلْيَنْظُرِ الْإِنْسَانُ إِلَىٰ طَعَامِهِ﴾

ሰውም ወደ ምግቡ ይመልከት፡፡

﴿أَنَّا صَبَبْنَا الْمَاءَ صَبًّا﴾

እኛ ውሃን ማንቧቧትን ያንቧቧን መኾናችንን፡፡

﴿ثُمَّ شَقَقْنَا الْأَرْضَ شَقًّا﴾

ከዚያም ምድርን (በደካማ ቡቃያ) መሰንጠቅን የሰነጠቅን፤

﴿فَأَنْبَتْنَا فِيهَا حَبًّا﴾

በውስጧም እኽልን ያበቀልን፤

﴿وَعِنَبًا وَقَضْبًا﴾

ወይንንም፤ እርጥብ ያበቀልን፤

﴿وَزَيْتُونًا وَنَخْلًا﴾

የዘይት ወይራንም ዘንባባንም፤

﴿وَحَدَائِقَ غُلْبًا﴾

ጭፍቆች አትክልቶችንም፤

﴿وَفَاكِهَةً وَأَبًّا﴾

ፍራፍሬንም ገለባንም፤ (ያበቀልን መኾናችንን ይመልከት)፡፡

﴿مَتَاعًا لَكُمْ وَلِأَنْعَامِكُمْ﴾

ለእናንተም ለእንስሶቻችሁም መጠቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን ሠራን)፡፡

﴿فَإِذَا جَاءَتِ الصَّاخَّةُ﴾

አደንቋሪይቱም (መከራ) በመጣች ጊዜ፤

﴿يَوْمَ يَفِرُّ الْمَرْءُ مِنْ أَخِيهِ﴾

ሰው ከወንድሙ በሚሸሽበት ቀን፤

﴿وَأُمِّهِ وَأَبِيهِ﴾

ከናቱም ካባቱም፤

﴿وَصَاحِبَتِهِ وَبَنِيهِ﴾

ከሚስቱም ከልጁም፤

﴿لِكُلِّ امْرِئٍ مِنْهُمْ يَوْمَئِذٍ شَأْنٌ يُغْنِيهِ﴾

ከእነርሱ ለየሰው ሁሉ በዚያ ቀን (ከሌላው) የሚያብቃቃው ኹነታ አልለው፡፡

﴿وُجُوهٌ يَوْمَئِذٍ مُسْفِرَةٌ﴾

ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፤

﴿ضَاحِكَةٌ مُسْتَبْشِرَةٌ﴾

ሳቂዎችም ተደሳቾችም ናቸው፡፡

﴿وَوُجُوهٌ يَوْمَئِذٍ عَلَيْهَا غَبَرَةٌ﴾

ፊቶችም በዚያ ቀን በላያቸው ላይ ትቢያ አልለባቸው፤

﴿تَرْهَقُهَا قَتَرَةٌ﴾

ጥቁረት ትሸፍናቸዋለች፤

﴿أُولَٰئِكَ هُمُ الْكَفَرَةُ الْفَجَرَةُ﴾

እነዚያ እነሱ ከሓዲዎቹ አመጸኞቹ ናቸው፡፡

الترجمات والتفاسير لهذه السورة: