المرسلات

تفسير سورة المرسلات

الترجمة الأمهرية

አማርኛ

الترجمة الأمهرية

ترجمة معاني القرآن الكريم للغة الامهرية ترجمها الشيخ محمد صادق ومحمد الثاني حبيب . الطبعة 2011م. ملاحظة: ترجمات بعض الآيات (مشار إليها) تم تصويبها بمعرفة مركز رواد الترجمة، مع إتاحة الاطلاع على الترجمة الأصلية لغرض إبداء الرأي والتقييم والتطوير المستمر.

﴿بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَٰنِ الرَّحِيمِ وَالْمُرْسَلَاتِ عُرْفًا﴾

ተከታታይ ኾነው በተላኩት፣

﴿فَالْعَاصِفَاتِ عَصْفًا﴾

በኀይል መንፈስን ነፋሾች በኾኑትም፣

﴿وَالنَّاشِرَاتِ نَشْرًا﴾

መበተንን በታኞች በኾኑትም፤ (ነፋሶች)፣

﴿فَالْفَارِقَاتِ فَرْقًا﴾

መለየትን ለይዎች በኾኑትም፣

﴿فَالْمُلْقِيَاتِ ذِكْرًا﴾

መገሠጫን (ወደ ነቢያት) ጣይዎች በኾኑትም፣

﴿عُذْرًا أَوْ نُذْرًا﴾

ምክንያትን ለማስወገድ ወይም ለማስፈራራት (ጣይዎች በኾኑት መላእክት) እምላለሁ፡፡

﴿إِنَّمَا تُوعَدُونَ لَوَاقِعٌ﴾

ያ የምትስፈራሩበት (ትንሣኤ) በእርግጥ ኋኝ ነው፡፡

﴿فَإِذَا النُّجُومُ طُمِسَتْ﴾

ከዋክብትም (ብርሃንዋ) በታበሰች ጊዜ፡፡

﴿وَإِذَا السَّمَاءُ فُرِجَتْ﴾

ሰማይም በተከፈተች ጊዜ፡፡

﴿وَإِذَا الْجِبَالُ نُسِفَتْ﴾

ጋራዎችም በተንኮተኮቱ ጊዜ፡፡

﴿وَإِذَا الرُّسُلُ أُقِّتَتْ﴾

መልክተኞቹም ወቅት በተደረገላቸው ጊዜ፡፡

﴿لِأَيِّ يَوْمٍ أُجِّلَتْ﴾

ለየትኛው ቀን ተቀጠሩ (የሚባል ሲኾን)፤

﴿لِيَوْمِ الْفَصْلِ﴾

ለመለያው ቀን (በተባለ ጊዜ፤ በፍጡሮች መካከል ይፈረዳል)፡፡

﴿وَمَا أَدْرَاكَ مَا يَوْمُ الْفَصْلِ﴾

የመለያውም ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?

﴿وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِلْمُكَذِّبِينَ﴾

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

﴿أَلَمْ نُهْلِكِ الْأَوَّلِينَ﴾

የፊተኞቹን (ሕዝቦች) አላጠፋንምን?

﴿ثُمَّ نُتْبِعُهُمُ الْآخِرِينَ﴾

ከዚያም የኋለኞቹን እናስከትላቸዋለን፡፡

﴿كَذَٰلِكَ نَفْعَلُ بِالْمُجْرِمِينَ﴾

በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሠራለን፡፡

﴿وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِلْمُكَذِّبِينَ﴾

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

﴿أَلَمْ نَخْلُقْكُمْ مِنْ مَاءٍ مَهِينٍ﴾

ከደካማ ውሃ አልፈጠርናችሁምን?

﴿فَجَعَلْنَاهُ فِي قَرَارٍ مَكِينٍ﴾

በተጠበቀ መርጊያ ውስጥም (በማሕፀን) አደረግነው፡፡

﴿إِلَىٰ قَدَرٍ مَعْلُومٍ﴾

እስከ ታወቀ ልክ ድረስ፡፡ መጠንነውም፤ ምን ያማርንም

﴿فَقَدَرْنَا فَنِعْمَ الْقَادِرُونَ﴾

መጠንነውም፤ ምን ያማርንም መጣኞች ነን!

﴿وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِلْمُكَذِّبِينَ﴾

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

﴿أَلَمْ نَجْعَلِ الْأَرْضَ كِفَاتًا﴾

ምድርን ሰብሳቢ አላደረግናትምን?

﴿أَحْيَاءً وَأَمْوَاتًا﴾

ሕያዋን ኾናችሁ ሙታንም ኾናችሁ፡፡

﴿وَجَعَلْنَا فِيهَا رَوَاسِيَ شَامِخَاتٍ وَأَسْقَيْنَاكُمْ مَاءً فُرَاتًا﴾

በውስጧም ከፍተኛዎችን ተራራዎች አደረግን፡፡ ጣፋጭ ውሃንም አጠጣናችሁ፡፡

﴿وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِلْمُكَذِّبِينَ﴾

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

﴿انْطَلِقُوا إِلَىٰ مَا كُنْتُمْ بِهِ تُكَذِّبُونَ﴾

«ወደዚያ በእርሱ ታስተባብሉ ወደ ነበራችሁት (ቅጣት) አዝግሙ፡፡

﴿انْطَلِقُوا إِلَىٰ ظِلٍّ ذِي ثَلَاثِ شُعَبٍ﴾

«ባለ ሦስት ቅርንጫፎች ወደ ኾነው ጥላ አዝግሙ፤» (ይባላሉ)፡፡

﴿لَا ظَلِيلٍ وَلَا يُغْنِي مِنَ اللَّهَبِ﴾

አጠላይ ያልኾነ ከእሳቱም ላንቃ የማያድን ወደ ኾነው (አዝግሙ)፡፡

﴿إِنَّهَا تَرْمِي بِشَرَرٍ كَالْقَصْرِ﴾

እርሷ እንደ ታላላቅ ሕንጻ የኾኑን ቃንቄዎች ትወረውራለች፡፡

﴿كَأَنَّهُ جِمَالَتٌ صُفْرٌ﴾

(ቃንቄውም) ልክ ዳለቻዎች ግመሎችን ይመስላል፡፡

﴿وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِلْمُكَذِّبِينَ﴾

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

﴿هَٰذَا يَوْمُ لَا يَنْطِقُونَ﴾

ይህ የማይናገሩበት ቀን ነው፡፡

﴿وَلَا يُؤْذَنُ لَهُمْ فَيَعْتَذِرُونَ﴾

ይቅርታም ይጠይቁ ዘንድ፤ ለእነርሱ አይፈቀድላቸውም፡፡

﴿وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِلْمُكَذِّبِينَ﴾

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

﴿هَٰذَا يَوْمُ الْفَصْلِ ۖ جَمَعْنَاكُمْ وَالْأَوَّلِينَ﴾

ይህ መለያው ቀን ነው፡፡ እናንተንም የፊተኞቹንም ሰብሰብናችሁ፡፡

﴿فَإِنْ كَانَ لَكُمْ كَيْدٌ فَكِيدُونِ﴾

ለናንተም (ለማምለጥ) ብልሃት እንዳላችሁ ተተናኮሉኝ፡፡

﴿وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِلْمُكَذِّبِينَ﴾

ላስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

﴿إِنَّ الْمُتَّقِينَ فِي ظِلَالٍ وَعُيُونٍ﴾

ጥንቁቆቹ በጥላዎችና በምንጮች ውስጥ ናቸው፡፡

﴿وَفَوَاكِهَ مِمَّا يَشْتَهُونَ﴾

ከሚከጅሉትም ሁሉ በፍራፍሬዎች ውስጥ ናቸው፡፡

﴿كُلُوا وَاشْرَبُوا هَنِيئًا بِمَا كُنْتُمْ تَعْمَلُونَ﴾

«ትሠሩት በነበራችሁት ዋጋ የምትደሰቱ ኾናችሁ ብሉ፣ ጠጡም፤» (ይባላሉ)፡፡

﴿إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجْزِي الْمُحْسِنِينَ﴾

እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡

﴿وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِلْمُكَذِّبِينَ﴾

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

﴿كُلُوا وَتَمَتَّعُوا قَلِيلًا إِنَّكُمْ مُجْرِمُونَ﴾

ብሉ፤ ጥቂትንም (ጊዜ) ተጠቀሙ፡፡ እናንተ አመጸኞች ናችሁና፡፡

﴿وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِلْمُكَذِّبِينَ﴾

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

﴿وَإِذَا قِيلَ لَهُمُ ارْكَعُوا لَا يَرْكَعُونَ﴾

«ለእነርሱ ስገዱም» በተባሉ ጊዜ አይሰግዱም፡፡

﴿وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِلْمُكَذِّبِينَ﴾

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

﴿فَبِأَيِّ حَدِيثٍ بَعْدَهُ يُؤْمِنُونَ﴾

ከእርሱም ሌላ በየትኛው ንግግር ያምናሉ?

الترجمات والتفاسير لهذه السورة: